ስለ ፍቅር ብዬ
ሁሉን ነገር ችዬ
ባበዛ ዝምታ
ንቀቱ በረታ
ንፁህ ልቤን ወግቶ
ውስጠቴን አድምቶ
ጥሎኝ ከመንገዱ
ጊዚያት ነጎዱ
በጥላቻው ጥልቀት
በበደሉም ር'ቀት
ዓይኔ እንባ አፈለቀ
አካሌን ጠመቀ
ሠው በሚሉት ካህን
ዙሪያውን ሲታጠን
ገብቼ ከወንዙ ሕይወት ከሚሉቱ
ዕንባ ሆኖኝ ጠበል ተነከርኩኝ ውሥጡ
ጠልቄ ብወጣ
አዲስ ፀሐይ ወጣ
ዛሬ እኔም ተካንኩ
ደግነትን ጣልኩ
ሥለ ሠው-ልጅ ክፋት ውሥጤ ተሠበረ
እርኩሠት ተረጨ ክፋትን ዘመረ
yitesam ዘ- ሐረር
wow
ReplyDeleteTnx
ReplyDelete