Friday, March 14, 2014

አምሣለ ዮርዳኖስ


ስለ ፍቅር ብዬ
 ሁሉን ነገር ችዬ 
ባበዛ ዝምታ 
ንቀቱ በረታ
 ንፁህ ልቤን ወግቶ 
ውስጠቴን አድምቶ 
ጥሎኝ ከመንገዱ 
ጊዚያት ነጎዱ
 በጥላቻው ጥልቀት
 በበደሉም ር'ቀት
 ዓይኔ እንባ አፈለቀ
 አካሌን ጠመቀ
 ሠው በሚሉት ካህን 
ዙሪያውን ሲታጠን 
 ገብቼ ከወንዙ ሕይወት ከሚሉቱ 
ዕንባ ሆኖኝ ጠበል ተነከርኩኝ ውሥጡ
 ጠልቄ ብወጣ 
አዲስ ፀሐይ ወጣ 
 ዛሬ እኔም ተካንኩ
 ደግነትን ጣልኩ 
 ሥለ ሠው-ልጅ ክፋት ውሥጤ ተሠበረ
 እርኩሠት ተረጨ ክፋትን ዘመረ

 yitesam ዘ- ሐረር

2 comments: