Saturday, June 23, 2018

ብላቴናው እና ሙሴ

ያለግዜው የተዘመረ !!!
      ብላቴናው እና ሙሴ

ቴዲ አፍሮ ዘመን በማይሽረው ዜማ ያልገባቸውና ከህሊናቸው መታረቅ ያቃታቸው እንደሚሉት "ቁጣና አመጽ " ሳይሆን  ፍቅርና ተግሳጽ ያዘለ ምክርን  ጃ ያስተሰርያል ሲል
ህዝብ ልብ ከገባ እነሆ 13 ዓመታት ።
በግዜው ስልጣን ላይ የነበሩት ሰወች የመጡበትን ዓላማና ያለፉበትን መንገድ ረስተው ህዝብን ሲያስጨንቁና ሲያሸብሩ ህዝብም ልዪነቱ ውበት እንጂ መጥፊያው እንዳልሆነ በማመን በአንድነት "በመደመር"  በሕብረትና በቅንጅት ሆ ብሎ የወጣበት ብዙ እልቂትም የነበረበት መሆኑ አይረሳም።
ብላቴናው ያኔ
በ17 መርፌ በጠቀመው ቁምጣ
ፀጉሩን ያጎፈረው ዙፋን ላይ ሲወጣ
እንዳምናው ባለቀን ያምናውን ከቀጣ
አዲስ ንጉስ እንጂ ለውጥ መቼ መጣ
ሲል ድምፁን ከፍ አደረገ
ብዙወች ይሄን ቃል እንደ ስድብ ያዩታል ነገር ግን ስድብ አይደለም ለ17 አመት ልብሳቸው በላያቸው እስኪያልቅ ለነፃነት የታገሉ ሰወች ዓላማቸውን ረስተው እንደ ቀድሞው አፋኝ ስለሆኑ እንዲነቁ ነበር ጥሪው
ለዛም ነው መደምደሚያው
ይቅር በለውና የበደለን ወቅሰህ
ምህረት አስተምረን አንድ አርገን መልሰህ
  ጃ ያስተሰርያል
የሆነው
ይህ ብቻም አይደለም ብላቴናው
ኤሎሄ ኤሎሄ ላማ ሰበቅታኒ
ኧረ አይበቃም ወይ  ኢትዮጵያዬ
ብሎ ሲፀልይና እጁን ወደላይ ሲያነሳ
ፈጣሪ የሕዝቡን እንባ አይቶ እንደሚመልስ በቃ ብሎ ያን የተመኘውን ሰላምና እርቅ እንደሚያመጣ አንድነታችንም እንደሚመለስ
ሙሉ እምነት ነበረው ለዚህም ነበር አሳይተው የነሱንን እርቅና ሰላም ባየ ጊዜ
አበባ አየሽ ወይ? ለምለም
አበባ አየህ ወይ? ለምለም
ብሎ ያዜመው
ዳግም ተጠምዝዘው ሰላሙን ባያደፈርሱት
የብላቴናው ዝማሬ  ዘመኑን ጀመርነው ይኸው ታርቀን -------ለዓለም እንዳይለያየን ዘለዓለም  ብሎ ማዜሙ ምነኛ ያማረ ነበር ? ነገር ግን ቢዘገይ እንጂ አልቀረምና ያ ያለግዜው የተዜመው ዜማ አሁን ላይ ከፍ ተደርጎ ይከፈት አበባ አየህ ወይ?  አዎ እኔ አይቻለው ያውም ለምለም!!!!
አሁን የብላቴናው ፀሎት ተሰምቷል
 
ዘ-ፀሃት ለኢትዮጵያ ወደ ተስፋ ጉዞ
ባህሩን ሚያሻግር አንድ ሙሴን ይዞ
ቅርብ ነው አይርቅም የኢትዮጵያ ትንሳኤ
ባንድነት ከገባን የፍቅር ሱባኤ 


     

ዶክተር አብይ  የፀሎታችን ፍጻሜ እንዲሆንና  ኢትዮጵያችንን ይዞ እንደሙሴ  ወደፊት የሚሻገርበት ዘመን እንዲሆን ተመኘሁ 


    እናንትስ ?  አበባ አየህ ወይ ?
                      አበባ አየሽ ወይ?

የዳህላኩም ህልማችን እውን ይሆናል ገና !!!!!!!!!

1 comment: