Sunday, July 29, 2018

የፍቅር ጮራ

ባጨለሙት ሰማይ
በገዙት ምድር ላይ
የክፋት ዘር ዘርተው
አንዱን ሐረግ ባንዱ እየጠመዘዙ
                          ዘመናት ተጓዙ
የቀመሩት ቀመር
የሸረቡት ሴራ ድንግዝግዝ ፈጠረ
አንዱ ግንድ ከሌላው ፍትጊያ ጀመረ
ሐገር ጽልመት ዋጣት
ጨለማ ነገሰ
ሌባው ተመችቶት የልቡ ደረሰ

ጨለማ ነው ብሎ እንዳሻው ሲጋልብ
ያሻውን ሲያደርግ
አንዱ አንዱን እንዲጥል ሲያፋትግ ሲያፋትግ

ከፍትጊያው መሃል እሳት ብልጭ አለ
ብርሃን ፈነጠቀ
እውነተኛው ጠላት ተለየ ታወቀ
በደም መስተፋቅር ሐረግ ተዋደደ
አንድነት ነገሰ ሰላም ተወለደ
የነፃነት ፋና ጮራ ፈነጠቀ
ሰውነት ከበረ ሰውነት ደመቀ

Friday, July 13, 2018

ኩኩ መለኮቴ

            ( ጉጉ)  ኩኩ መለኮቴ
ፍርድ ተበደለ
ፍትህ ተጓደለ
አቤቱታ ሰሚ ቅን ፈራጅ ሰው ጠፋ
አህያው እያለ ዳውላው ተገፋ

ኩኩ መለኮቴ የብሶት ጩኸቴ
ፍርድ መማጸኛ በልጅ አንደበቴ
ዛሬ ሰሚን ቢያገኝ ላዚመው በርጅና
ካንቀላፉት መሃል ንቁ አይጠፋምና

ኩኩ ኩኩ ኩኩ
ኩኩ መለኮቴ
ጉርሻ ያነቀው ሰው
ዳግም አይበላም ወይ ?
ንገሩኝ በሞቴ

ያድነኛል ያለው መድሃኒት ቢያቆስለው
ባንድነት ፈርጆ
መድሃኒት ሁሉ መርዝ ብሎ ይላል ውይ ሰው?

ኩኩ ኩኩ ኩኩ
ኩኩ መለኮቴ
እሷ "ባጠፋችው"
በኔ ላከከችው

Tuesday, July 3, 2018

ያንተ ስፌት

ያንተ ስፌት

ለኔ ያልኩት ሁሉ
አንዳንዱ እየሰፋ
ሌላ እየጠበበኝ
የሚሆነኝ ጠፍቶ
ይኸው ራቆቴን ነኝ
……………………………………
ልክ ማውቅ መስሎኝ
ምኞት ተከትዬ
ያንተን መልካም ፈቃድ
በስሜቴ ጥዬ
ይኸው አሁን ድረስ
ብቀድም ብሰፋ
ከዚህ ሁላ ምኞት
የሚሆነኝ ጠፋ
………………………………
ስለዚህ አባቴ
ፍቃድህ እውነት ነው
አንተው ጨርስልኝ
የኔ ምኞት ረዝሟል
ባንተ መልካም ፈቃድ
በልኬ ስፋልኝ

                  ከልዑል ሀይሌ
@getem
@getem
@lula_al_greeko

ፍቅር ያሸንፋል!!!!!

ሳያውቁ በስህተት.......
የ 28 ዓመታቱ አገዛዝ በጣም በሚገርም ሁኔታ ድምጽ አልባ አቢዮት ተካሂዶበት የተገለበጠና ያበቃለት ይመስላል።
በደም የተገኘ ስልጣን በደም ካልሆነ ከእጅ አይወጣም የሚለውን መፈክር ያፈረሰ ታላቅ ትግል ታላቅ ድል ይዞ መጥቷል ።
ነገር ግን በነዚያ ሁሉ ጊዜያት የተዘራው መርዝ በ አንዲት ጀንበር ይጠራል ማለት ባይቻልም የሚጠበቅ ጥቂት ለውጥ ግን መታየት አለበት።

በርግጥ ይህ ጥቂት ብዬ ያስቀመጥኩት ለውጥ ታላቅና ለሐገራችን ህልውና እና ለምንጠብቀው እድገት ወሳኝ መሰረት ነው።
ታዲያ ለምን ጥቂት ለውጥ አልክ ካላቹኝ ግን ምክንያቱም ይህ ለውጥ በዶክተር አብይ አህመድ እና በአመራራቸው ሊመጣ ስለማይችልና ይልቁንም ከያንዳዳችን ኢትዮጵያውያን ግለሰቦች የሚጠበቅ በመሆኑ ነው።

ይህ ለውጥ ምንድነው? ካልን ደግሞ ከዘረኝነት የፀዳ! አመለካከትን ማዳበር ነው።
ጠቅላይ ሚንስተር ዶክተር አብይ መንገዱን አሳይተውናል በዘር መርጠው ሳይሆን እያንዳንዱን ኢትዮጵያዊ ወደው አንድነትና ፍቅርን ሰብከዋል ።

ይህን ጥሪ አለመቀበል ግን ሳያውቁ በስህተት  የነበረውን አፋኝ አገዛዝ እሳቤ ማራመድ ነው
ምክንያቱም ዓላማቸው አንድ እና አንድ የኢትዮጵያን ሕዝብ በዘርና በሐይማኖት እያጋጩ የስልጣን ጊዜን ማራዘምና ወንበራቸው ከተገፋ ህዝቡን ማጫረስ ስለሆነ።

ደስ የሚለው ግን ስልጣናቸው አብቅቷል ሕዝቡም አንድነትን መርጧል በዚ ሁሉ ሁኔታ ውስጥ  ያለፈበትን ሀሳብ ለማራመድ ዘር እየጠቀሱ መሳደብና ልዩነትን ለመፍጠር መሞከር ያስገርማል ይህን የምታደርጉ ሰዎች ሳታውቁት ከሆነ ስህተት መሆኑን ተረዱ ሆን ብላቹ ከሆነ ግን ህዝብ አንድነትን መርጧልና አትልፉ ነን ብላቹ የምትለጥፉትንም ብሄር አታውቁትም አትወክሉትምም!!!!