Tuesday, July 3, 2018

ፍቅር ያሸንፋል!!!!!

ሳያውቁ በስህተት.......
የ 28 ዓመታቱ አገዛዝ በጣም በሚገርም ሁኔታ ድምጽ አልባ አቢዮት ተካሂዶበት የተገለበጠና ያበቃለት ይመስላል።
በደም የተገኘ ስልጣን በደም ካልሆነ ከእጅ አይወጣም የሚለውን መፈክር ያፈረሰ ታላቅ ትግል ታላቅ ድል ይዞ መጥቷል ።
ነገር ግን በነዚያ ሁሉ ጊዜያት የተዘራው መርዝ በ አንዲት ጀንበር ይጠራል ማለት ባይቻልም የሚጠበቅ ጥቂት ለውጥ ግን መታየት አለበት።

በርግጥ ይህ ጥቂት ብዬ ያስቀመጥኩት ለውጥ ታላቅና ለሐገራችን ህልውና እና ለምንጠብቀው እድገት ወሳኝ መሰረት ነው።
ታዲያ ለምን ጥቂት ለውጥ አልክ ካላቹኝ ግን ምክንያቱም ይህ ለውጥ በዶክተር አብይ አህመድ እና በአመራራቸው ሊመጣ ስለማይችልና ይልቁንም ከያንዳዳችን ኢትዮጵያውያን ግለሰቦች የሚጠበቅ በመሆኑ ነው።

ይህ ለውጥ ምንድነው? ካልን ደግሞ ከዘረኝነት የፀዳ! አመለካከትን ማዳበር ነው።
ጠቅላይ ሚንስተር ዶክተር አብይ መንገዱን አሳይተውናል በዘር መርጠው ሳይሆን እያንዳንዱን ኢትዮጵያዊ ወደው አንድነትና ፍቅርን ሰብከዋል ።

ይህን ጥሪ አለመቀበል ግን ሳያውቁ በስህተት  የነበረውን አፋኝ አገዛዝ እሳቤ ማራመድ ነው
ምክንያቱም ዓላማቸው አንድ እና አንድ የኢትዮጵያን ሕዝብ በዘርና በሐይማኖት እያጋጩ የስልጣን ጊዜን ማራዘምና ወንበራቸው ከተገፋ ህዝቡን ማጫረስ ስለሆነ።

ደስ የሚለው ግን ስልጣናቸው አብቅቷል ሕዝቡም አንድነትን መርጧል በዚ ሁሉ ሁኔታ ውስጥ  ያለፈበትን ሀሳብ ለማራመድ ዘር እየጠቀሱ መሳደብና ልዩነትን ለመፍጠር መሞከር ያስገርማል ይህን የምታደርጉ ሰዎች ሳታውቁት ከሆነ ስህተት መሆኑን ተረዱ ሆን ብላቹ ከሆነ ግን ህዝብ አንድነትን መርጧልና አትልፉ ነን ብላቹ የምትለጥፉትንም ብሄር አታውቁትም አትወክሉትምም!!!!

No comments:

Post a Comment