ያንተ ስፌት
ለኔ ያልኩት ሁሉ
አንዳንዱ እየሰፋ
ሌላ እየጠበበኝ
የሚሆነኝ ጠፍቶ
ይኸው ራቆቴን ነኝ
……………………………………
ልክ ማውቅ መስሎኝ
ምኞት ተከትዬ
ያንተን መልካም ፈቃድ
በስሜቴ ጥዬ
ይኸው አሁን ድረስ
ብቀድም ብሰፋ
ከዚህ ሁላ ምኞት
የሚሆነኝ ጠፋ
………………………………
ስለዚህ አባቴ
ፍቃድህ እውነት ነው
አንተው ጨርስልኝ
የኔ ምኞት ረዝሟል
ባንተ መልካም ፈቃድ
በልኬ ስፋልኝ
ከልዑል ሀይሌ
@getem
@getem
@lula_al_greeko
No comments:
Post a Comment