እግር አንፈራጦ
እጅ አጥፎ ተቀምጦ
ከቶ ምን ሊመጣ ምን ከምን ተገኝቶ
አውጣኝ ያለ ወጣ አብላኝ ያለም በላ
ተኝቶ የዋለ አሳማ ተበላ
ቢሆንም ብሂሉ
ወዲ እኮ ነው ቅሉ
አብላኝ ያለ አንበሳ
ለአደን ተነሳ
ጫካውን አሰሰ
የድካሙን ዋጋ ፍሬውን አፈሰ
አውጣኝ ያለ ፈረስ
ጠላት ከሱ እንዳይደረስ
ሮጠ ፈረጠጠ
በጠንካራ እግሮቹ
ከመጣበት መቅሰፍት ጥፋት አመለጠ
ስንፍና ተጭኖት የተኛው አሳማ
የጠላትን መድረስ በፍፁም ሳይሰማ
ሩቅ እንደተመኘ እሩቅ እንዳለመ
ጥቂት ሳይራመድ በሞት ተቀደመ
እናም
ይህ ነው ሕይወት ቅሉ
እሩጡ ውጡ እንጂ አውጣን አትበሉ
Samson mekonnen
No comments:
Post a Comment